Psalm 142 | In Amharic and English (with Amharic MP3)
መዝሙረ ዳዊት Mezmure Dawit
Psalms Of David #142
In Amharic and English
መዝሙረ ዳዊት 142 |
Psalm 142 |
1 በቃሌ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ በቃሌ ወደ እግዚአብሔር ለመንሁ። |
1 I cried unto the Lord with my voice; with my voice unto the Lord did I make my supplication. |
2 ልመናዬን በፊቱ አፈስሳለሁ መከራዬንም በፊቴ እናገራለሁ። |
2 I poured out my complaint before him; I shewed before him my trouble. |
3 ነፍሴ በውስጤ ባለቀች ጊዜ መንገዴን አወቅሁ በምሄድባት በዚያች መንገድ ወጥመድን ሰወሩብኝ። |
3 When my spirit was overwhelmed within me, then thou knewest my path. In the way wherein I walked have they privily laid a snare for me. |
4 ወደ ቀኝ ተመለከትሁ አየሁም፥ የሚያውቀኝም አጣሁ መሸሸጊያም የለኝም፥ ስለ ነፍሴም የሚመራመር የለም። |
4 I looked on my right hand, and beheld, but there was no man that would know me: refuge failed me; no man cared for my soul. |
5 አቤቱ፥ ወደ አንተ ጮኽሁ። አንተ ተስፋዬ ነህ፥ በሕያዋንም ምድር አንተ እድል ፈንታዬ ነህ አልሁ። |
5 I cried unto thee, O Lord: I said, Thou art my refuge and my portion in the land of the living. |
6 እጅግ ተቸግሬአለሁና ወደ ልመናዬ አድምጥ በርትተውብኛልና ከሚያሳድዱኝ አድነኝ። |
6 Attend unto my cry; for I am brought very low: deliver me from my persecutors; for they are stronger than I. |
7 አቤቱ፥ ስምህን አመሰግን ዘንድ ነፍሴን ከወህኒ አውጣት ዋጋዬን እስክትሰጠኝ ድረስ ጻድቃን እኔን ይጠብቃሉ። |
7 Bring my soul out of prison, that I may praise thy name: the righteous shall compass me about; for thou shalt deal bountifully with me. |